የቢሮዉ ኃላፊ   መልዕክት

 

ff

 

                                                        አቶ ማቶ ማሩ 

የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ፍትህ ቢሮ መስሪያ ቤት በሐምሌ ወር 2012 . በአዋጅ ቁጥር 6/2012 የተቋቋመ ሲሆን በህግ የተሰጠውን ሃላፊነትና ተግባር በመወጣት በመልካም አስተዳደርና በዲሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ አስፈላጊውን ተሳትፎ በማድረግ በክልላችን ብሎም በሀገር ደረጃ አስተማማኝ ፍትህና የዲሞክራሲ ስርዓት ለማረጋገጥ በሚደረግ ጥረት ውስጥ ከፍተኛ ድርሻ ያለው መሆኑ ይታወቃል፡፡

በመሆኑም ተቋማችን ግልፅ የሆነ 10 አመቱን መሪ እቅድና 2013 በጀት አመት እቅድ በመንደፍ በተግባር ለመፈፀም ሰፊ ርብርብ በማድረግ እስከ ታችኛው መዋቅር ባሉ አደረጃጀቶች በአገልግሎት አሰጣጥ እርካታን ለማምጣት ግልፅነት የተላበሰ፤ቀልጣፋና ፍትሐዊና  ተጠያቂነት የሰፈነበት አሰራርን መዘርጋት ትኩረት በማድረግ የሚገጥሙ የኪራይ ሰብሳቢነት አመለካከትና ተግባራትን ለመከላከል የህግ ተጠያቂነትን በማረጋገጥ ችግሮች ለመፍታት በሚደረገው ጥረት ውስጥ የክልላችን ህብረተሰብ በአገልግሎት አሰጣጣችን ላይ የሚያነሳቸውን ቅሬታዎችና ጥያቄዎች ለማድመጥ እነዚህን ችግሮች የሚፈቱበት ሳይንሳዊ የሆነ  የአሰራርና ስልቶችን በመቀየስ ቀጣይነት ያለው  የአሰራር ስርዓት በመገንባት  መልካም አስተዳደር እና የህግ የበላይነት እንዲሰፍን መስራት እና ከህዝብ ተሳትፎ የሚገኙ ግብዓቶችንና አስተያየቶችን የመፍትሄ አካል ማድረግ ያስፈልጋል፡፡

እንዲሁም በየደረጃው ያለው የሰው ሐይል የተሰጠውን ተልዕኮ በተገቢው መንገድ የተረዳና የሚተገብር ዜጋንና ተገልጋይን የሚያከብር መልካም ስነ- ምግባር ያለውና ተልኮውን አሟልቶ መፈፀም የሚያስችል ፈፃሚን መገንባት እና የመፈፀም ብቃቱን በየግዜው የማሳደግ  ጉዳይ ትኩረት ሊደረግበት የሚገባ ተግባር ነው፡፡   

                                      See More